Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ደቡብ ኮሪያ ባለሃብቶቿ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥረት እንደምታደርግ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ደቡብ ኮሪያ ባለሃብቶቿ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ አስፈላጊውን ጥረት እንደምታደርግ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ልዩ መልዕክተኛ ተናገሩ፡፡

የደቡብ ኮሪያ ፕሬዚዳንት ዩን ሶክ ዮል ልዩ መልዕክተኛ ጃንግ ሱንግ ሚን እንዳሉት÷ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ኮሪያ በግድ እና ኢኮኖሚ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡

ሀገራቱ በተይም በኢንቨስትመንት ዘርፍ ያላቸውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እቅድ ተዘጋጅቶ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የደቡብ ኮሪያ መንግስት የሀገሪቱ ተጨማሪ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ፍላጎት እንዳለውም አረጋግጠዋል፡፡

ለዚህም ባለሃብቶቹ ቢሰማሩ ውጤታማ ሊሆኑ የሚችሉባቸው የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት የሥራ ሃላፊዎች ጋር ምክክር መደረጉን ጠቁመዋል፡፡

ባለሃብቶቹ በጤና፣ በትራንስፖር እና በማምረቻው ዘርፍ በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ እና በኢትዮጵያ ያለውን እምቅ ሃብት በተመለከተ መረጃ እንደሚሰጣቸውም አንስተዋል፡፡

አሁን ላይ የደቡብ ኮሪያ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙም ነው የተናገሩት።

 

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version