Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መቃኞ ቤተ ክርስቲያን መረቁ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ብፁዕ ወ ቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ-ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በአቡዳቢ የኢትዮጰያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መቃኞ ቤተ ክርስቲያንን መርቀው መንፈሳዊ አገልግሎት አስጀመሩ።

የቤተ ክርስቲያኑ መቃረቢያ ቤት ዛሬ በተመረቀበት ወቅት ቡራኬ የሰጡት ቅዱስ ፓትርያርኩ ÷ “በምትፈልጉት ጊዜ ከፍታችሁ የምትገቡበት ቤ/ክ ስላገኛችሁ ደስ ብሎናል ፤ ይህንን የሚያህል ስፋት ያለውም አይቼ አላውቅም” ብለዋል።

በዕለቱ ሀገረ ስብከቱ ለግንባታ ቦታ መረከብና ለጊዜያዊ ቤተ ክርስትያን መታነጽ አስተዋፅዖ ለነበራቸው አካላት የምሥጋና እና ዕውቅና የመስጠት ሥርዓት መከናወኑን በተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version