Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ 2 አዳዲስ አባላትን አካተተ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ ሁለት አዳዲስ አባላትን በኮሚቴው ውስጥ አካትቷል።

ፓርቲው በተለያዩ ምክንያቶች በተጓደሉ የሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ምትክ ነው አዳዲስ አመራሮችን በኮሚቴው አባልነት የመደበው፡፡

በዚህ መሠረትም አቶ አብዱ ሁሴን እና አቶ ይርጋ ሲሳይ ኮሚቴውን በአባልነት መቀላቀላቸውን የፓርቲው መረጃ ያመላክታል።

አመራሮቹ የረጅም ዓመት የፖለቲካ ልምድ ያካበቱ እና ፓርቲው የጀመረውን ሀገራዊና አካታች የብልጽግና ጉዞ እንደሚያግዙ መታመኑ ተጠቁማል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version