Fana: At a Speed of Life!

የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ 2 አዳዲስ አባላትን አካተተ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ ሁለት አዳዲስ አባላትን በኮሚቴው ውስጥ አካትቷል።

ፓርቲው በተለያዩ ምክንያቶች በተጓደሉ የሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ምትክ ነው አዳዲስ አመራሮችን በኮሚቴው አባልነት የመደበው፡፡

በዚህ መሠረትም አቶ አብዱ ሁሴን እና አቶ ይርጋ ሲሳይ ኮሚቴውን በአባልነት መቀላቀላቸውን የፓርቲው መረጃ ያመላክታል።

አመራሮቹ የረጅም ዓመት የፖለቲካ ልምድ ያካበቱ እና ፓርቲው የጀመረውን ሀገራዊና አካታች የብልጽግና ጉዞ እንደሚያግዙ መታመኑ ተጠቁማል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.