Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በብሔራዊ ባንክ እና ስዊድን ማዕከላዊ ባንክ መካከል የትብብር ስምምነት ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እና በስዊድን ማዕከላዊ ባንክ (ሪክስ ባንክ) ገዥ መካከል የትብብር ስምምነት በዛሬው ዕለት ተፈርሟል፡፡

የትብብር ስምምነቱ ÷ የቴክኒክ፣ የምርምር፣ የኮሙኒኬሽን እና ዲጂታይዜሽን ትብብሮችን እንደሚያካትት መገለጹን የብሔራዊ ባንክ መረጃ ያመላክታል፡፡

የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምኅረቱ÷ የብሔራዊ ባንክ ማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ወደነበረበት ለመመለስ እና መዋቅራዊ ማሻሻያዎችን እንደገና ለማነቃቃት እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን አብራርተዋል፡፡

በሌላ በኩል ስታንዳርድ ባንክ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ከበርካታ የውጭ ባንኮችና የፋይናንስ ተቋማት ኃላፊዎች ጋር ተወያይቷል።

Exit mobile version