አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) የ16 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ሥምምት ተፈራርመዋል፡፡
ሥምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና የኮይካ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶንግሆ ኪም ተፈራርመዋል፡፡
የድጋፍ ስምምነቱ የግብርና ዘርፉን ወጪ ንግድ ለማበረታታት እና የህጻናት መቀንጨርን መቀነስ እንደሚያስችል መገለጹን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡