Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያ እና ኮይካ የ16 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ሥምምት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) የ16 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ሥምምት ተፈራርመዋል፡፡

ሥምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና የኮይካ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶንግሆ ኪም ተፈራርመዋል፡፡

የድጋፍ ስምምነቱ የግብርና ዘርፉን ወጪ ንግድ ለማበረታታት እና የህጻናት መቀንጨርን መቀነስ እንደሚያስችል መገለጹን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version