Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ እና ኮይካ የ16 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ሥምምት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና የኮሪያ ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) የ16 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ሥምምት ተፈራርመዋል፡፡

ሥምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና የኮይካ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶንግሆ ኪም ተፈራርመዋል፡፡

የድጋፍ ስምምነቱ የግብርና ዘርፉን ወጪ ንግድ ለማበረታታት እና የህጻናት መቀንጨርን መቀነስ እንደሚያስችል መገለጹን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.