Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሊቢያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

 

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሊቢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱልሃሚድ አልዳባቢያ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷ “የሊቢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱልሃሚድ አልዳባቢያን በመቀበሌ ደስታ ተሰምቶኛል”ብለዋል።

በውይይታቸውም በቀጠናዊ የሰላም እና መረጋጋት፣ የኢኮኖሚ ትብብር፣ የሰው ሃይል ልውውጥ እና ሌሎች የጋራ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ተናግረዋል፡፡

የሊቢያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብዱልሃሚድ አልዳባቢያ በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ትናንት ምሽት አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል፡፡

Exit mobile version