Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ በቀድሞ የኬንያ ፕሬዚዳንት ዳንኤል አራፕ ሞይ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ

አዲስ አበባ ፣ ጥር 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በቀድሞ የኬንያ ፕሬዚዳንት ዳንኤል አራፕ ሞይ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክትም ለኬንያውያን መጽናናትን ተመኝተዋል።

ከኬንያ ነጻነት በኋላ ሁለተኛው የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት በመሆን ለ24 ዓመታት ሀገሪቱን የመሩት ዳንኤል አራፕ ሞይ በ95 ዓመታችው ማረፋቸው ተነግሯል።

Exit mobile version