Fana: At a Speed of Life!

ዶክተር ሊያ እና የጣሊያን አምባሳደር የጤናውን ዘርፍ ለማጠናከር የሚያስችል ውይይት አካሄዱ

አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እና በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር አጎስቲኖ ፓሌሴ በጤናው ዘርፍ የሚደረገውን ትብብር ለማጠናከር የሚያስችል ውይይት ማካሄዳቸው ተገለጸ፡፡

በውይይታቸውም ሀገራቱ በጤናው ዘርፍ የሚያደርጉትን ትብብር ለማጠናከር እና በኮቪድ -19 ወረርሽኝ ላይ በትብብር መሥራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

ሚኒስትሯ ጣሊያን በጤናው ዘርፍ ለኢትዮጵያ ለምታደርገው ያላሰለሰ ሙያዊ ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

አምባሳደር አጎስቲኖ ፓሌሴ በበኩላቸው ÷ ኢትዮጵያ እና ጣሊያ ን በጤናው ዘርፍ ያላቸው ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡

ጣሊያን በኮቪድ-19 ላይ የምታደርገውን ድጋፍም አጠናክራ እንደምትቀጥል አምባሳደሩ ማረጋገጣቸውን በኢትዮጵያ ከጣሊያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.