Fana: At a Speed of Life!

ኢጋድ በምስራቅ አፍሪካ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ትሥሥር ዕውን ለማድረግ ይሠራል-ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በቀጠናው ተጨባጭ የኢኮኖሚ ትሥሥር ዕውን ለማድረግ እንደሚሠራ የድርጅቱ ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ ተናገሩ።

ዋና ጸሃፊው በብራስልስ በተካሄደው የአፍሪካ ቀንድ የሚኒስትሮች ኢኒሼቲቭ ስብሰባ ላይ ተካፍለዋል፡፡

በስብሰባውም ዶክተር ወርቅነህ፥ የኢኒሼቲቩን አራት ምሰሶዎች ማለትም ቀጠናዊ የመሠረተ-ልማት ትሥሥር፣ የተሳለጠ የንግድ ከባቢ፣ ለውጫዊ ተጽዕኖ ምላሽ የመስጠት ችሎታ እንዲሁም የቀጠናውን ሀገራት ኢኮኖሚ ለማሳደግ የሰው ኃብት የማበልፀግ አስፈላጊነት ላይ ማብራሪያ መስጠታቸውን የኢጋድ ሥራ አስፈጻሚ ጽህፈት ቤት ቃል አቀባይ ኑር ሞሐሙድ ሼክ ጠቁመዋል፡፡

በእነዚህ ምሰሶዎች ላይ መሥራትም ቀጠናዊ ተጽዕኖን ለመቋቋም እንደሚያግዝ ዶክተር ወርቅነህ ማስገንዘባቸውንም ሥራ አስፈጻሚው በትዊተር ገፃቸው በኩል አስታውቀዋል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.