Fana: At a Speed of Life!

ራሱን የጋምቤላ ነፃነት ግንባር ብሎ የሚጠራው ድርጅት ዋና የጦሩ መሪ ሆኖ ሲሰራ የነበረው ግለሰብ ለመንግስት እጁን ሰጠ

አዲስ አበባ የካቲት 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋምቤላ ክልል ራሱን የጋምቤላ ነፃነት ግንባር (ጋነግ) ብሎ የሚጠራው ድርጅት ዋና የጦሩ መሪ ሆኖ ሲሰራ የነበረው ግለሰብ አቶ ዛን ዱዌር በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለመንግስት እጁን ሰጠ።

ግለሰቡ ቀደም ሲል የክልሉ መንግስት ባደረገው ሰላማዊ ጥሪ ተከትሎ በአካባቢው ጎሳ መሪዎች አማካኝነት ወደ ህዝቡ መመለስ መቻሉ ተጠቅሷል።

የጋምቤላ ነፃነት ግንባር ( ጋነግ) ድርጅት የጦሩ መሪ ሆኖ ሲሰራ የነበረው አቶ ዛን ዱዌር በተሳሳተ መንገድ ወደ ጫካ በመግባት የትጥቅ ትግል ሲያደርግ እንደነበር ተመልክቷል።

መንግስት ያደረገውን የሠላም ጥሪ ተከትሎ ወደ አካባቢው የተመለሰው ግለሠብ ከመንግስት ጋር በመሆን ተገቢው ክትትል እየተደረገ መሆኑን ከክልሉ መንግስት ፕረስ ሴክሬታሪያት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.