Fana: At a Speed of Life!

“ለኢትዮጵያ እንቁም” የተሰኘ ዘመቻ በለንደን ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 23 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለንደን በተከበረው 126ኛው የዓድዋ ድል በዓል የመታሰቢያ መርሃ-ግብር ላይ “ለኢትዮጵያ እንቁም” የተሰኘ ዘመቻ ተካሄደ፡፡

የኢትዮጵያ የዓለም ፌዴሬሽን የተሰኘ የጥቁሮች ህዝቦች የሆነ ድርጅት ዘመቻውን መምራቱን በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡

በለንደን የኢፌዴሪ አምባሳደር ተፈሪ መለስ በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙ ሲሆን ይህን ሠናይ ተግባር ላዘጋጁ አካላት ልባዊ ምሥጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

አምባሳደሩ የዓድዋ ድል በዓል ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካውያን ነጻነትም የላቀ ሥፍራ አለው ብለዋል፡፡

በዓድዋ ድል በዓል የመታሰቢያ መርሃ-ግብር ላይ የተለያዩ ማኅበረሰቦችን የሚወክሉ ቡድኖች፣ ድርጅቶች እና በዩናይትድ ኪንግደም የራስ ተፈሪያን ንቅናቄ አባላት ተገኝተዋል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.