Fana: At a Speed of Life!

የብፁዕ አቡነ መርቆሬዎስ አስከሬን የሽኝትና የቀብር ስነ-ስርዓት የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ አስከሬን ሽኝትና ለቀብር ስነ ስርዓት ዝግ የሚሆኑና ተለዋጭ መንገዶችን ይፋ ማድረጉን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡

የሽኝቱና የቀብር ስነ-ስርዓቱ በሰላም እንዲከናወን የፀጥታ አካላት አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡

ቅዳሜ መጋቢት 3 ቀን 2014 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ የፓትርያርኩ አስከሬን ሽኝት የሚካሄድና የቀብር ስነ-ስርዓታቸውም መጋቢት 4 ቀን 2014 ዓ.ም በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የሚፈፀም ይሆናል፡፡

ነገ መጋቢት 3 ቀን 2014 ዓ.ም የሚካሄደው የአስከሬን ሽኝት ፕሮግራም ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ዝግ የሚሆኑና ተለዋጭ መንገዶችን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡

በዚሁ መሠረትም፡-

 ከቦሌ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ

 ከመገናኛ ፣በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያን አካባቢ

 ከአራት ኪሎ ፣ በውጭ ጉዳይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት

 ከፒያሳ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሐራምቤ ሆቴል መብራት

 ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር

 ከጦር ኃይሎች ፣ በሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ለገሃር መብራት ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከቀኑ 12:30 ጀምሮ ዝግጅቱ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ፡፡

በዕለቱምየብፁእነታቸው አስከሬን ከመስቀል አደባባይ ወደ መንበረ ፓትርያርክ (ቅድስት ማሪያም ቤተ ክርስቲያን) በሚንቀሳቀስበት ወቅት ከመስቀል አደባባይ ፣ በብሔራዊ ቤተ መንግስት፣ ውጭ ጉዳይ ፣ አራት ኪሎ፣ ቅድስት ማርያም የሚወስደው መንገድ መጋቢት 4 ቀን 2014 ዓ.ም የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ የቀብር ስነ-ስርዓት የሚፈፀም በመሆኑ የቀብር ስነ-ስርዓቱ እስከሚፈፀም ወደ ቅድስት ማርያም፣ አራት ኪሎ እና ስላሴ ቤተ-ክርስቲያን የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሰጡት አማራጭ መንገዶችን መጠቀም እንዳለባቸው ተገልጿል፡፡

በተጨማሪም ለጋራ ደህንነት ሲባል በሽኝቱ እና በቀብር ስነ-ስርቱ ወቅት ፍተሻ መኖሩን የፕሮግራሙ ታዳሚዎች ተገንዝበው ለፀጥታ አካላት አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አሳስቧል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.