Fana: At a Speed of Life!

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ25ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በባህር ዳር ስታዲየም በተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ኦኪኪ ኦፎላቢ በ3ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠራት ግብ ፋሲል ከነማ ወሳኝ 3 ነጥብ ማግኘት ችሏል፡፡

አፄዎቹ ዛሬ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ፋሲል ከነማ በ49 ነጥብ ከፕሪምየር ሊጉ መሪ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ያላቸውን የነጥብ ልዩነት ወደ 5 ማጥበብ ችለዋል፡፡

በአንፃሩ ፈረሰኞቹ ከ24 ጨዋታዎች በኋላ የመጀመሪያ ሽንፈታቸውን ሲያስተናግዱ፥ ከ8 ጨዋታዎች በኋላም የመጀመሪያ ግብ ተቆጥሮባቸዋል፡፡

ረፋድ ላይ የተደረገው የወላይታ ዲቻ እና የአርባምንጭ ከተማ ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.