የአፍሪካ ኅብረት ልዩ የመሪዎች ጉባዔ መካሄድ ጀመረ
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 19 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ኅብረት ልዩ የመሪዎች ጉባዔ በኢኳቶሪያል ጊኒ ዋና ከተማ ማላቦ እየተካሄደ ነው።
ጉባዔው በሰብአዊ እርዳታና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል።
በተጨማሪም ፀረ ሽብር ጉዳዮች ላይ እና ኢ-ሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ሥልጣን ለመያዝ የሚደረጉ ጥረቶችን መከላከል በሚቻልበት አግባብ ላይ ይመክራል ተብሎም ይጠበቃል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጉባኤው ለመሳተፍ በትናንትናው እለት ማላቦ መግባታቸው የሚታወስ ነው።