Fana: At a Speed of Life!

የአፍሪካ ኅብረት ልዩ የመሪዎች ጉባዔ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 19 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ኅብረት ልዩ የመሪዎች ጉባዔ በኢኳቶሪያል ጊኒ ዋና ከተማ ማላቦ እየተካሄደ ነው።

ጉባዔው በሰብአዊ እርዳታና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል።

በተጨማሪም ፀረ ሽብር ጉዳዮች ላይ እና ኢ-ሕገ መንግሥታዊ በሆነ መንገድ ሥልጣን ለመያዝ የሚደረጉ ጥረቶችን መከላከል በሚቻልበት አግባብ ላይ ይመክራል ተብሎም ይጠበቃል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጉባኤው ለመሳተፍ በትናንትናው እለት ማላቦ መግባታቸው የሚታወስ ነው።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.