Fana: At a Speed of Life!

አቶ ደመቀ መኮንን አዲስ ከተሾሙት የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሚካኤል ሀመርን ጋር ተወያይተዋል ።

በውይይታቸውም በሰሜን የኢትዮጵያ ክፍል በግጭት ለተጎዱ አካባቢዎች የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦትን እንዲሁም በግጭቱ ወቅት ለተፈጸሙ በደሎች ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እየተወሰዱ ባሉ እርምጃዎች እና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

አቶ ደመቀ በውይይቱ መንግሥት ወደ ትግራይ እርዳታ ለሚያጓጉዙ ሰብዓዊ አጋሮች ያልተገደበ ተደራሽነትን ለማመቻቸት ያለውን ቁርጠኝነት ገልፀዋል።

በሽብርተኛው ህወሓት ወረራ ምክንያት በአፋር እና አማራ ክልሎች ለተፈናቀሉ እና ለችግር ለተዳረጉ ዜጎች የሰብአዊ አጋር ድርጅቶች ድጋፍ እንዲያደርጉም መጠየቃቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሚካኤል ሀመር በበኩላቸው÷ ወደ ትግራይ ክልል እየተደረገ ያለው የሰብአዊ አቅርቦት ፍሰት እንዳስደነቃቸው ገልፀዋል ወደ ክልሉ የገቡትን የእርዳታ አቅርቦት የጫኑ መኪኖችን በማንሳት፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.