Fana: At a Speed of Life!

ድምጻዊ ዳዊት ነጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 6 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ድምጻዊ ዳዊት ነጋ (ድአመና) ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
ድምጻዊው ከአራት ቀናት በፊት ባጋጠመው ድንገተኛ የጤና እክል በአዲስ ህይወት ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ትናንት ምሽት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ድምፃዊ ዳዊት ነጋ “ወዛመይ”፣ “ዘዊደሮ”፣ “ቸኮላታ” “ብነፀላይ” እና “ባባኢለን” በተባሉ ዘፈኖቹ በብዙዎች ዘንድ ይታወቃል።
ድምፃዊ ዳዊት ነጋ ባለትዳር እና የልጆች አባት ነበር፡፡
የድምፃዊው የቀብር ስነ ስርዓትም ነገ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ይፈጸማል፡፡
ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ለመላው ቤተሰቡ፣ ወዳጅ ዘመዶቹና አድናቂዎቹ መፅናናትን ይመኛል።
በማህሌት ተ/ብርሃን
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.