ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ የተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽ ሰጡ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው የተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባው፥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰጡትን ምላሽና ማብራሪያ አዳምጧል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እየሰጡት ባሉት ምላሽ÷ ባለፉት አራት ዓመታት የተከሰቱ ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ልናሳካው ያሰብነውን ዕቅድ በታሰበለት ልክ እንዳይሄድ አድርገውታል ብለዋል፡፡