Fana: At a Speed of Life!

የግብርና ሥራዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚገባ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የግብርና ሥራዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ይገባል ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ተናገሩ፡፡

የክልሉ ግብርና ቢሮ የ2014/2015 ምርት ዘመን የባለድርሻ አካላት የንቅናቄ መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እያካሄደ ነው።

በዚሁ ወቅት እንደተገለጸውም÷ በክልሉ በ2014/2015 የመኸር ወቅት ከ14 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል፡፡

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር ለግብርናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ጠቅሰው÷ ክልሉ ካለው ምቹ ስነ ምህዳር አንጻር በ2013/14 የምርት ዘመን የተገኘው አፈጻጸም ዝቅተኛ መሆኑን አንስተዋል፡፡

አፈጻጸሙን ለማሻሻልም በአንዳንድ ዞኖች የተጀመሩ የግብርና ሜካናይዜሽን ሥራ በሌሎችም ዞኖች እንዲሰፋ ጥረት ይደረጋል ብለዋል።

የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው÷ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የግብርና ሜካናይዜሽን ሥራዎችን በመተግበር የክልሉን የመልማት አቅም አሟጦ መጠቀም እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡

የግብርና ሥራዎችን በማዘመን እና የቴክኖሎጂ ሽግግር በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ እንደሚገባም ተገልጿል፡፡

በ2014/2015 የመኸር ወቅት ከ350 ሺህ በላይ ሔክታር መሬት በማልማት÷ ከ14 ሚሊየን በላይ ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ግብ መያዙን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.