Fana: At a Speed of Life!

የዴንማርክ መንግስት በኢትዮጵያ ንጹሕ የመጠጥ ውሃ ለማዳረስ 10 ሚሊየን ዶላር ለገሰ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዴንማርክ መንግስት በኢትዮጵያ ንጹሕ የመጠጥ ውሃ በዘላቂነት ለማዳረስ የሚውል 10 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር መለገሱን ዩኒሴፍ ኢትዮጵያ ገልጿል፡፡

ዩኒሴፍ ኢትዮጵያ፥ የዴንማርክ መንግስት ላደረገው ድጋፍ ትልቅ ምሥጋና አቅርቦ ፣ ንጹሕ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር በኢትዮጵያ በዘላቂነት ለመፍታት የሚደረገውን ጥረትም ላለፉት ሦስት ዓመታት ሲያግዝ መቆየቱን አስታውሷል፡፡

የዴንማርክ መንግስት በኢትዮጵያ አምባሳደር ኪራ ስሚዝ ሲንድበርግ ÷ በሶማሌ ክልል የተከሰተው ድርቅ ያሳደረውን ተጽዕኖ አውስተው በክልሉ የሚገኙ ሴቶች እና ሕፃናትን ሕይወት ለማሻሻል ንጹሕ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እጅግ አስፈላጊ ነው ማለታቸውን ከዩኒሴፍ ኢትዮጵያ የትዊተር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.