Fana: At a Speed of Life!

የአፍሪካ ልማት ባንክ በተለያዩ የልማት ዘርፎች ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በአጋርነት እንደሚቀጥል ተገለጸ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 17 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ልማት ባንክ በወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የተለያዩ የልማት ዘርፎች ላይ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በአጋርነት እንደሚቀጥል ተገለጸ፡፡

የሥራና ክህሎት ሚንስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ በአፍሪካ ልማት ባንክ የምሥራቅ አፍሪካ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱል ካማራ ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገናል ብለዋል፡፡

ባንኩ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በትብብር በሚሠራበት ማዕቀፍ ላይ መወያያታቸውንም ገልጸዋል፡፡

የአፍሪካ ልማት ባንክ÷ በክህሎት ልማት፣ በወጣቶች ሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለወጣት ሥራ ፈጣሪዎች የፋይናንስ ድጋፍና ተደራሽነት እንዲሁም በመሰል የትብብር መስኮች ላይ የልማት አጋር ሆኖ እንደሚቀጥል ማረጋገጡንም ነው ወይዘሮ ሙፈሪያት የገለጹት፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.