Fana: At a Speed of Life!

ተሸናፊው ውርስ ችግር ሊያሳምመን እንጂ ሊያሸንፈን አይችልም – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ተሸናፊው ውርስ ችግር ሊያሳምመን እንጂ ሊያሸንፈን አይችልም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ ኢትዮጵያ ከነባር ችግሮቿ ተላቅቃ በተስፋዋ ጎዳና እንድትገሠግሥ እየታገልን ነው ብለዋል፡፡
ያለፈው ችግሯ ውርስም መከራችንን ሊያረዝመው ይታገለናል፤ እኛ ደግሞ ተስፋችንን ለማለምለም እንታገላለን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ÷ በችግራችን ከተዋጥን ይነግሥብናል፤ ለተስፋችን ከታገልን ደግሞ እንነግሥበታለን ብለዋል፡፡
ተሸናፊው ውርስ ችግር ሊያሳምመን እንጂ ሊያሸንፈን አይችልምም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመልዕክታቸው፡፡
በዚህ እሑድ ሁላችንም መቻቻልና አብሮነት እንዲያሸንፍ እንጸልይ÷ ነጋችን ብሩህ እንዲሆን ደግሞ ወጥተን ዛፎችን እንትከል ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.