Fana: At a Speed of Life!

በ11 ወራት ከ2 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል – የደቡብ ምዕራብ  ክልል ገቢዎች ቢሮ

 

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 11 ወራት ውስጥ ከ2 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ፡፡

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የ2014/15 የግብር ከፋዮች የግብር አከፋፈል ንቅናቄ እየተካሄደ ነው፡፡

የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ህይወት አሰግድ በንቅናቄው ላይ እንደገለጹት÷ በ2014 ዓ.ም በክልሉ በተከለሰው ዕቅድ መሰረት ከ2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ለመሰብሰብ ታቅዶ ሲሰራ ቆይቷል፡፡

በ 11 ወራት ውስጥም ለመሰብሰብ ከታቀደው 2 ነጥብ 58 ቢሊየን ብር 2 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን ጠቁመው÷ከተሰበሰበው ገቢም አብዛኛው ከመንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ሰራተኞች የተገኘ ነው ብለዋል፡፡

በ2014/2015 የግብር መክፈያ ወቅት ከሀምሌ እስከ ጥቅምት ከደረጃ ሐ፣ ለ እና ሀ ግብር ከፋዮች 238 ሚሊየን 780 ሺህ 588 ብር ለመሠብሰብ መታቀዱንም ነው ወይዘሮ ህወት አሰግድ የተናገሩት፡፡

የደቡብ ምዕራብ  ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመንግስት ተጠሪ አቶ ጸጋዬ ማሞ÷ ክልሉ በሀብቱ መጠቀም እንዲችል ጠንካራ የግብር አሰባሰብ ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

መሠረተ ልማትን በማሟላትና ኢንቨስትመንትን በመሳብ ክልሉን ማልማት የሚቻለው ካለው ሀብት በአግባቡ ገቢን መሠብሰብ ሲቻል ነው ብለዋል፡፡

በተስፋዬ ምሬሳ

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.