Fana: At a Speed of Life!

የቡድን 7 አባል ሀገራት በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሚመክር የመወያያ ክበብ ለመመስረት ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቡድን 7 አባል ሀገራት መሪዎች የዓለም ሙቀት መጨመርን ለመግታት የሚመክር የመወያያ ክበብ ለመመስረት ተስማምተዋል፡፡

ክበቡ ፈቃደኛ የሆኑ ሀገራትን በማስተባበር የዓለም ሙቀት መጨመርን መቋቋም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ እንደሚሰራ በመግለጫቸው አስታውቀዋል፡፡

የፓሪሱን የዓየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ለመተግበር ቁርጠኛ የሆኑ ሀገራትን በአባልነት ለማቀፍ ክበቡ ክፍት መሆኑም ነው የተነገረው፡፡

በተለይ ክበቡ ከኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሚመነጭ በካይ ጋዝ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥና ሀገራትና ኢንዱስትሪዎቻቸው ለዓለም አቀፉ ህግ እንዲገዙ እንደሚሰራ የቡድን 7 አባል ሀገራት መሪዎች የሦስት ቀናት ጉባዔያቸውን ሲያጠናቅቁ በሰጡት መግለጫ ማስታወቃቸውን ሲ ጂ ቲ ኤን ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.