Fana: At a Speed of Life!

በነሐሴ ወር የ “ኦፔክ” አባል ሀገራት እና አጋሮቻቸው የነዳጅ ምርታቸውን ለማሳደግ ተሥማሙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የነዳጅ አምራችና ላኪ ሀገራት እንዲሁም አጋሮቻቸው የሚያመርቱትን የነዳጅ መጠን በቀን በ648 ሺህ በርሜል ለማሳደግ ሥምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡

ሩሲያ በተጣለባት ማዕቀብ ምክንያት የነዳጅ ምርቷን ለመቀነስ ተገዳ መቆየቷ የሚታወስ ሲሆን፥ “ኦፔክ” እና አጋሮቻቸው ያመቻቹትን ዕድል በማዕቀብ ያጣችውን ገቢ ለማካካስ ልትጠቀምበት ትችላለችም ነው እየተባለ ያለው፡፡

የ“ኦፔክ” አባል ሀገራትና አጋሮቻቸው ነዳጅ ላይ የተፈጠረውን የዋጋ ንረት ምርታቸውን በማሳደግ እንዲያረጋጉ ከምዕራባውያኑ ጥሪ ቀርቦላቸው ባሳለፍነው ግንቦት ወር ላይ ውድቅ ማድረጋቸውን ሲጂቲ ኤን በዘገባው አስታውሷል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.