ከሳዑዲ ዓረቢያ 1ሺህ 59 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት በሦስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን የመመለስ ሥራ በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1ሺህ 59 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡
ከተመለሱት መካከል÷ 63 ሕጻናት፣ 196 ሴቶች እና 800 ወንዶች መሆናቸውን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
ለተመላሽ ዜጎችም ተገቢው ድጋፍ እና እንክብካቤ ተደርጎላቸው ወደ ተዘጋጀላቸው የማቆያ ማዕከላት እንዲሄዱ መደረጉም ተገልጿል፡፡
እስካሁን ድረስ በተከናወነ ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ሥራ÷ 46 ሺህ 384 ኢትዮጵያውያን መመለሳቸውን መረጃው አመላክቷል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!