የማዕድን ሚኒስቴር ከቱርክ ኩባንያዎች ጋር ሶስት የመግባቢያ ሰነዶችን ተፈራረመ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕድን ሚኒስቴር ከቱርክ ኩባንያዎች ጋር ሦስት የመግባቢያ ሰነዶችን ተፈራረመ፡፡
የማዕድን ሚኒስትሩ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንደገለጹት÷ የመግባቢያ ሰነዶቹ በተፈጥሮ ጋዝ ፍለጋና ልማት፣ በማዳበሪያ ፋብሪካ ማቋቋም እና በወርቅ ምርት ሥራዎች ላይ ትብብር ለማድረግ የሚያስችሉ ናቸው፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!