ኢትዮጵያ ለምታስተናግደው ዓለም አቀፉ የኢንተርኔት አስተዳደር ጉባኤ የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተጠናቀቀ መሆኑ ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ለምታስተናግደው ዓለም አቀፉ የኢንተርኔት አስተዳደር ጉባኤ የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተጠናቀቀ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የአለም አቀፉ የኢንተርኔት አስተዳደር ዝግጅት የባለ ብዙ ባለድርሻ አካላት አማካሪ ቡድን ስብሰባውን በጄኔቭ እያካሄደ ነው።