በአዲስ አበባ በተከሰተው ጭጋጋማ የአየር ፀባይ ምክንያት ተቋርጠው ከነበሩት በረራዎች አብዛኛዎቹ ተጀምረዋል – የኢትዮጵያ አየር መንገድ
አየር መንገዱ ባለፉት ጥቂት ሰአታት በአዲስ አበባ የነበረው ጭጋጋማ የአየር ፀባይ መሻሻል ማሳየቱን ጠቁሟል።
ከዚህ ጋር ተያይዞም መዳረሻቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ በረራዎች አብዛኛዎቹ መደረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።
በተጨማሪም ከአዲስ አበባ ተነስተው ወደ ተለያዩ ሃገራት የሚደረጉ በረራዎች ተጀምረዋልም ነው ያለው።
አያይዞም ለደንበኞቹ ተጨማሪ መረጃዎች ማድረሱን እንደሚቀጥልም ገልጿል።