Fana: At a Speed of Life!

ቦሪስ ጆንሰንን ለመተካት 8 ዕጩዎች ቀረቡ

አዲስ አበባ፣ሀምሌ 6 ፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የእንግሊዙን ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰንን ለመተካት ሥምንት ዕጩዎች መቅረባቸውን ጉዳዩን የያዘው የምርጫ አስፈጻሚ ኮሚቴ ገልጿል፡፡

ለእንግሊዙ ወግ አጥባቂ ፓርቲ በመሪነት ለመወዳደር ዕጩ ሆነው የቀረቡት ÷ ሪሺ ሱናክ፣ ሊዝ ትሩስ፣ ኬሚ ባዴኖች፣ ፔኒ ሞርዳውንት፣ ሱኤላ ብራቨርማን፣ ጄረሚ ሀንት፣ ናዲም ዘሃዊ እና ቶም ቱገንድሃት መሆናቸውን ኮሚቴው አስታውቋል፡፡

ሳጂድ ጃቪድ እና ሬህማን ቺሽቲ የተባሉት ዕጩዎች በምርጫው የመወዳደር ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸው የነበረ ቢሆንም  ፣ የመጨረሻው የዕጩዎች ዝርዝር ከመገለጹ በፊት  ራሳቸውን ከውድድሩ ስለማግለላቸው ተገልጿል፡፡

የመጀመሪው ዙር ውድድር በዛሬው ዕለት የሚጀመር ሲሆን ፣ ዕጩዎቹ ወደ መጨረሻው የመሪነት ውድድር ዝርዝር ውስጥ ለመግባት ቢያንስ 20 ድምፆችን ማግኘት እንደሚጠበቅባቸው ሲጂቲ ኤን ዘግቧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.