Fana: At a Speed of Life!

በ2014 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ 4 ነጥብ 12 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ተገኘ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2014 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ 4 ነጥብ 12 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር መገኘቱን የንግድን ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ሚኒስቴሩ በበጀት ዓመቱ ከወጪ ንግድ 4 ነጥብ 63 ቢሊየን የአሜሪካን ለማግኘት አቅዶ ነው 4 ነጥብ 12 ቢሊየን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉ ተገልጿል፡፡

አፈጻጸሙ ባለፈው በጀት ዓመት ከተገኘው 3 ነጥብ 62 ቢሊየን ዶላር የ13 ነጥብ 81 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተጠቁሟል፡፡

አጠቃላይ ከተያዘው የወጪ ንግድ ገቢ እቅድ አንፃር የግብርናው ዘርፍ 72 በመቶ ገቢ በማስገኘት ከፍተኛውን ድርሻ የያዘ ሲሆን ፥ ማዕድን 14 በመቶ፣ ኢንዱስትሪ 12 በመቶ እንዲሁም ኤሌክትሪክ ሁለት በመቶ ገቢ ማስገኘታቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.