የገቢዎች ሚኒስቴር እና ጉምሩክ ኮሚሽን ለደቡብ ምዕራብ ክልል ከ53 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ
በተጨማሪም በካፋ ዞን ዋቻ ከተማ ለቦባ ቆጫ ትምህርት ቤት ጥገና የሚውል የ6 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡
የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቃበታ በርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር÷ የተፈጥሮ ሃብታችንን ጠብቆ ማልማት ይገባል ማለታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
ትምህርት ቤቶች ተተኪ ዜጎችን የምናፈራበት በመሆኑ ትውልዱን ለመንከባከብ የሚያስችል ድጋፍ አድርገናልም ነው ያሉት፡፡
የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፀጋዬ ማሞ በበኩላቸው÷ ተቋሙ ከዚህ ቀደምም ክልሉን በመርዳት ቀዳሚ መሆኑን ጠቅሰው አሁን ለተደረገው ድጋፍም አመስግነዋል።
ክልሉ በርካታ የወጪ ምርቶችና ማዕድናት የሚገኝበት በመሆኑ ሚኒስቴሩ በክልሉ ትኩረት አድርጎ እንዲሠራ ጠይቀዋል፡፡
የተሰጡንን ድጋፎች ለታለመለት ዓላማ አውለን ችግኞችንም ተንከባክበን ዕቅዳችንን ፍሬያማ እናደርጋለን ብለዋል፡፡