Fana: At a Speed of Life!

ሩሲያ ከዩክሬን ለሚከፈትባት ጥቃት ከባድ አፀፋዊ ምላሽ ትሰጣለች – ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የሩሲያ ፕሬዚዳንት ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ ዩክሬን ሀገራቸው ላይ ጥቃት ከከፈተች አፀፋዊ ምላሹ እጅግ የከፋ እንደሚሆን አስጠነቀቁ።

ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ አንዳንድ የዩክሬን ባለሥልጣናት ሩሲያን ለማስፈራራት በመገናኛ ብዙኃን መግለጫዎችን ሲሰጡ መታዘባቸውንና እና ድርጊታቸው የሚያስከትልባቸው መዘዝ እጅግ የከፋ እንደሚሆን መናገራቸውን አር ቲ ኒውስ ዘግቧል።

የዩክሬን የመከላከያ ሚኒስቴር የደኅንነት ክፍል ቃል አቀባይ ቫዲም ስኪቢትስኪ “በክሬሚያ ጥቁር ባሕር የሚገኙት የሩሲያ የጦር መርከቦች ለደኅንነታችን ስለሚያሰጉን በአሜሪካ-ሰራሽ ሮኬቶቻችን እንመታቸዋለን” ማለታቸው ይታወሳል።

ሜድቬዴም ዩክሬን ለምትፈጽመው ጥቃት ሞስኮ ከባድ አፀፋዊ መልስ ትሰጣለች ብለዋል።

ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ ከፈረንጆቹ 2008 እስከ 2012 ሩሲያን በፕሬዚዳንትነት መምራታቸው ይታወሳል።

በአሁኑ ወቅት የሀገሪቱ የጸጥታ ምክር ቤት ምክትል ሊቀመንበር ሆነው እያገለገሉ ይገኛሉ።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.