Fana: At a Speed of Life!

በሶማሊያ ከደረሰ የአውሮፕላን አደጋ መንገደኞች ከጉዳት ተረፉ

አዲስ አበባ፣ ሀምሌ11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) 30 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረው የሶማሊያ መንገደኞች አውሮፕላን በሞቃዲሾ አውሮፕላን ማረፊያ መከስከሱ ተዘግቧል፡፡

የአውሮፕላን ማሪፊያው ባለስልጣናት እንደገለፁት፥ አውሮፕላኑ ሞቃዲሾ አየር ማረፊያ እያረፈ በነበረበት ወቅት አደጋ ደርሶበት በግዳጅ ያረፈ ሲሆን፥ በመንገደኞች ላይ ምንም ጉዳት አልደረሰም፡፡

አውሮፕላኑ ሞቃዲሾ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ በኃይል ማረፉን ተከትሎ የእሳት ቃጠሎ መነሳቱንና አካባቢው በጭስ መሞላቱን ከስፍራው የወጡ ምስሎች ያሳያሉ፡፡

የጁባ ኤርዌይስ ንብረት የሆነው አውሮፕላኑ ከባይዶዋ ወደ ዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ የውስጥ በረራ እያደረገ እንደነበርም ዋሽንግተን ፖስት ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.