አትሌት ጎይተቶም ገብረስላሴ 3ኛውን የወርቅ ሜዳልያ ለኢትዮጵያ አስገኘች
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 11 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሪገን እየተካሄደ በሚገኘው 18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ተጨማሪ የወርቅ ሜዳልያ አገኘች።
ከሰአት በኋላ በተካሄደው የሴቶች የማራቶን ውድድር አትሌት ጎይተቶም ገብረስላሴ ውድድሩን በአሸናፊነት አጠናቃለች።
ርቀቱን 2 ሰአት ከ18 ደቂቃ ከ11 ሰከንድ በመግባት ነው አሸናፊ የሆነችው።
በዚህም የሻምፒዮናውን ክብረ ወሰን አሻሽላለች።
ኢትዮጵያም 3ኛውን የወርቅ ሜዳልያ በሻምፒዮናው አግኝታለች።
በውድድሩ የኬንያ እና የእስራኤል አትሌቶች 2ኛ እና 3ኛ በመሆን አጠናቀዋል።