Fana: At a Speed of Life!

የአማራ ክልል በጎ ፈቃደኞች አገልግሎት መርሐ ግብር በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የዘንድሮው የአማራ ክልል በጎ ፈቃደኞች አገልግሎት መርሐ ግብር በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ በሚል መሪ ሃሳብ በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ባንጃ ወረዳ ተጀምሯል፡፡

በፕሮግራሙ የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለን ጨምሮ የክልሉና የብሔረሰብ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በመርሐ ግብሩ ላይ ወጣቶች በክረምቱ ወቅት አረጋውያንን በመንከባከብ፣ ሕጻናትን በትምሕርት በማገዝና በደም እጦት የሰው ሕይወት እንዳያልፍ ደም በመለገስ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.