Fana: At a Speed of Life!

የአማራ ክልል ምክር ቤት የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል ምክር ቤት የተለያዩ ሹመቶችን አጽድቋል፡፡
በዚሁ መሠረት፡- አቶ እርዚቅ ኢሳ የአማራ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም አቶ ሰውበሰው ብዙአየሁ ደግሞ የክልሉ ምክትል ዋና ኦዲተር ሆነው ተሹመዋል፡፡
ምክር ቤቱ ለንጋት ኮርፖሬት የቦርድ አመራር ሹመቶች ያጸደቀ ሲሆን÷ አቶ ስዩም መኮንን የቦርድ ሰብሳቢ እና ወይዘሮ አይናለም ንጉሴ ደግሞ ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሹመዋል፡፡
ምክር ቤቱ ለአራት ቀናት በነበረው ቆይታ÷ “የተሻሻለው የአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ” እና “የተሻሻለው የአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች የዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ማቋቋሚያ አዋጅ” አጽድቋል፡፡
እንዲሁም÷ 95 ነጥብ 31 ቢሊየን ብር ሆኖ የቀረበውን የክልሉን መንግሥት የ2015 በጀትም አጽድቋል፡፡
የተያዘው በጀት÷ በህወሓት እና በሸኔ የሽብር ቡድን ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢዎችን መልሶ ለማቋቋም፣ ቅድሚያ ለሚሰጣቸው ለግብርና ኢንቨስትመንት፣ ለማዕድን ዘርፍ እና ለአካባቢ ጥበቃ ሥራ ትኩረት መስጠቱ ተመላክቷል፡፡
በምንይችል አዘዘው
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.