Fana: At a Speed of Life!

ሚድሮክ በ750 ሚሊየን ብር  የገነባው የ“ቺፕስ” ፋብሪካ ሥራ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ750 ሚሊየን ብር ወጪ በሐዋሳ ከተማ የገነባው የ“ቺፕስ” ፋብሪካ ተመርቆ ሥራ ጀመረ፡፡

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ ስፈፃሚ አቶ ጀማል አሕመድ በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት÷ ፋብሪካው በጀመሪያ ዙር ሥራው ለ242 ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል፡፡

ፋብሪካው በቀን 36 ቶን ድንች የመፍጨት አቅም እንዳለው ጠቁመው÷ ይህም በሐዋሳ ከተማና አካባቢዋ ለሚገኙ ድንች አምራች አርሶ አደሮች ተጠቃሚነት ከፍተኛ አስተዋፅዖ አለው ብለዋል፡፡

የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ፀጋዬ ቱኬ እንደገለጹት÷ ሚድሮክ በሐዋሳ ከተማ እያደረገ ያለው ኢንቨስትመንት የሥራ ዕድልን ከመፍጠር ባለፈ የከተማችንን ቱሪዝም ከፍ እንዲል አድርጓል።

ለኢንቨስትመንት መሬት ወስደው ያላለሙ ግለሰቦችና ተቋማት ወደ ልማት መግባት እንዳለባቸው አሳስበው÷ ወደ ከተማችን ለሚመጣ ማንኛውም አልሚ አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል፡፡

የ “ቺፕስ” ፋብሪከው ሠራተኞች በበኩላቸው÷ የችብስ ፋብሪካው በአካባቢው ያልተለመደ መሆኑን ጠቁመው አዲስ የሥራ ባህልን እንደሚያመጣ ተናግረዋል፡፡

በጥላሁን ይልማ

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.