Fana: At a Speed of Life!

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከአንጎላ ጠቅላላ ምርጫ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድንን የሚመሩት የቀድሞ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከአንጎላ ጠቅላላ ምርጫ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይተዋል፡፡

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በቅድመ ምርጫ ውይይታቸው የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ ከተለያዩ ምርጫ አስፈጻሚ አካላት ጋር መክረዋል።

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የአንጎላ ብሔራዊ ምርጫ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ዶክተር ማኑኤል ዳ ሲልቫንም ማነጋገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

የአንጎላ ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ረቡዕ እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.