Fana: At a Speed of Life!

የከፍተኛ ትምህርት አመራሮች ዓውደ ጥናት እየተካሔደ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አመራሮች የሁለት ቀናት የአመራር እና አስተዳደር ዓውደ ጥናት እየተካሄደ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ ጉዳይ ፈፃሚ አምባሳደር ትሬሲ አን ጃኮብሰን ÷ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራሮች በተዘጋጀው ዓውደ ጥናት ላይ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል፡፡

አምባሳደር ጃኮብሰን በመልዕክታቸው፥ ዓውደ ጥናቱ የኢትዮጵያ እና የአሜሪካን ዩኒቨርሲቲዎች አጋርነት የሚያጠናክር ነው ብለዋል።

ዓውደ ጥናቱ በመሪነት፥ በሥራ አመራርና በአስተዳደር ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር እንደሆነም በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.