Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያን 3ኛ ደረጃ ይዞ አጠናቀቀ

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 21 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ሴቶች ሻምፒዮንስ ሊግ የሴካፋ ዞን ማጣሪያ በሦስተኛነት አጠናቀቀ።

በማጣሪያው ላይ ኢትዮጵያን የወከለው ንግድ ባንክ ዛሬ በአዛም ኮምፕሌክስ ባደረገው የደረጃ ጨዋታ የርዋንዳውን ኤ ኤስ ኪጋሊን 3 ለ 1 በማሸነፍ ሦስተኛ ደረጃ ይዞ ማጠናቀቁን ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል።

አረጋሽ ካልሳ፣ ሀሳቤ ሙሶ እና ሎዛ አበራ ግቦቹን አስቆጥረዋል። የርዋንዳው ክለብ ጎል ሀሳቤ ሙሶ በራሷ ግብ ላይ አስቆጥራለች።

የውድድሩ አሸናፊ ሴካፋን ወክሎ በአፍሪካ ሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ ይሳተፋል።

ሁለተኛው የሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ በሞሮኮ አስተናጋጅነት በጥር ወር 2015 ዓ.ም ይካሄዳል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.