Fana: At a Speed of Life!

በሐረሪ ክልል እህትማማቾች ውኃ ውስጥ ሰጥመው ሕይወታቸው አለፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐረሪ ክልል ድሬ ጠያራ ወረዳ ሁለት እህትማማች ሕጻናት በጉድጓድ ውስጥ ከተጠራቀመ ውኃ ለመቅዳት ሲሞክሩ ባጋጠማቸው አደጋ ሰጥመው ሕይወታቸው አልፏል፡፡

የድሬ ጠያራ ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ እንደገለፁት÷ በወረዳው ገንደ ባላ ተብሎ በሚጠራ መንደር ውስጥ እህትማማቾቹ ለግብርና ሥራ ታስቦ ከተቆፈረ ጉድጓድ ውስጥ ውኃ ለመቅዳት ሲሞክሩ ሰጥመው ሕይወታቸው አልፏል፡፡

ውኃ ለመቅዳት ሲሞክሩ አንደኛዋ ወደ ውኃ ጉድጓዱ ውስጥ መግባቷን ተከትሎ ሌላኛዋ የገባችውን ለማውጣት ስትሞክር ሁለቱም ጉድጓዱ ውስጥ መስጠማቸውን የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን መረጃ አመላክቷል፡፡

በዚህ ወረዳ በተደጋጋሚ የሕጻናት ሕይወት በተመሳሳይ መልኩ እየጠፋ  በመሆኑ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አዛዡ አሳስበዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.