Fana: At a Speed of Life!

የጅማ ዞን ለመከላከያ ሠራዊት ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጅማ ዞን ነዋሪዎች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ከ30 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አድርገዋል፡፡

የጅማ ዞን ነዋሪዎች ከዚህ ቀደምም ለሠራዊቱ ተመሳሳይ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን ፥ የዛሬው ሁለተኛ ዙር መሆኑ ተመላክቷል።

የዞኑ ነዋሪዎች የሀገር ህልውናን ለማስከበር እየተዋደቁ ለሚገኘው የመከላከያ ሠራዊት በ30 ሚሊየን ብር ወጪ የሚገመት የአይነት ድጋፍ አድርገዋል፡፡

የተደረገው ድጋፍ ከ500 በላይ ሰንጋ በሬዎችን እና ሌሎች ምግብ ነክ ግብዓቶችን ያካተተ መሆኑን የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ትጃኒ ናስር ተናግረዋል፡፡

አስተዳዳሪው አሸባሪው ህወሓት ተደምስሶ የሀገር ሰላም እስኪረጋገጥ የዞኑ ነዋሪዎች የጀመሩትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

በአሊዳን መሃመድ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.