ከፍተኛ ባለስልጣናት በዝነኛው ከያኒ ማዲንጎ አፈወርቅ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ ባለስልጣናት በዝነኛው ከያኒ ማዲንጎ አፈወርቅ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ፡፡
የማዕድን ሚኒስትር ታከለ ኡማ÷ በድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ሕልፈት ሐዘን እንደተሰማቸው ገልጸው÷ ለቤተሰቦቹ፣ ወዳጆቹና አድናቂዎቹ መፅናናትን ተመኝተዋል፡፡
በተመሳሳይ ዶክተር ይልቃል ከፋለ አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ ለሀገሩና ለትውልድ ጥበብንና ባህልን አውርሶ ያለፈ እውቅ ከያኒ መሆኑን ገልጸው÷ የሚችለውን ሁሉ ለሚወዳት ሀገሩ ተቀኝቷል ብለዋል፡፡
በችግር ውስጥ ሆኖም ለኢትዮጵያ ነጻነትና ክብር ሲል ከጠላት ጋር የሚዋደቀውን ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችንን እና የጸጥታ ኃይላችንን ግንባር ድረስ ዘልቆ አበረታትቷል ነው ያሉት።
ስለኢትዮጵያ ቀደምት ስልጣኔና ታሪክ፣ ሰላምና አንድነት፣ ነጻነትና ክብር በርካታ የጥበብ ሥራዎችን መሥራቱን ጠቁመዋል፡፡
እንዲሁም ከንቲባ አዳነች አቤቤ÷ በአርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ ሕልፈተ ሕይወት ከልብ አዝኛለሁ ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል ተመስገን ጥሩነህ÷ ተወዳጁ አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ ማረፉን ስሰማ እጅግ ከባድ ሐዘን ተሰምቶኛል፤ አርቲስቱ ሀገሩን የሚወድና ለሀገሩ ሠለቸኝ ደከመኝ ሳይል በጽናት ብዙ የሠራ ነው ብለዋል፡፡
ባለስጣናቱ ለአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶቹ እና ለጥበብ አድናቂዎቹ በሙሉ መጽናናትን ተመኝተው÷ ፈጣሪ የአርቲስቱን ነፍስ በአጸደ ገነት ያኑር ብለዋል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!