Fana: At a Speed of Life!

ሰሜን ኮሪያ አጭር ርቀት ሚሳኤል አስወነጨፈች

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 12 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰሜን ኮሪያ አጭር ርቀት ሚሳኤል አስወነጨፈች።

ሚሳኤሉ ፒዮንግያንግ በዚህ ወር መጀመሪያ በድጋሚ የጀመረችው የሙከራ አካል ሲሆን፥ ወደ ጃፓን ባህር የተወነጨፈ ነው ተብሏል።

የጃፓን ባህር ሃይል በሃገሪቱ የባህር ክልል አቅራቢያ ሚሳኤል ማረፉን አስታውቋል።

ጎረቤት ደቡብ ኮሪያ በበኩሏ ተጨማሪ ሙከራዎች ካሉ በሚል ጉዳዩን እየተከታተልኩ ነው ብላለች።

የሃገሪቱ መከላከያ ባወጣው መግለጫ የኮሮና ቫይረስ የሃገራት ስጋት በሆነበት በዚህ ወቅት ሙከራ ማድረጉ ተገቢነት የሌለው መሆኑን ገልጿል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.