Fana: At a Speed of Life!

በፕሪሚየርሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲዳማ ቡናን 5 ለ 1 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲዳማ ቡናን 5 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል፡፡

በባህርዳር ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኢስማኤል ኦሮ አጉሮ ሀትሪክ ሲሰራ÷ በረከት ወልዴ እና አማኑኤል ገብረሚካኤል የጊዮርጊስን የማሸነፊያ ግቦች አስቆጥረዋል፡፡

ፈረሰኞች ሲዳማ ቡናን ማሸነፋቸውን ተከትሎ በ9 ነጥብ መሪነታቸውን አጠናክረዋል፡፡

በተመሳሳይ ወላይታ ዲቻ እና ኢትዮኤሌክትሪክ  በዛሬው ዕለት ያደረጉት ጨዋታ አንድ አቻ  በሆነ ውጤት ተጠናቋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.