Fana: At a Speed of Life!

ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው ባሻገር በማኅበረሰብ ተኮር ሥራዎች የበለጠ መሥራት አለበት- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ከመማር ማስተማር ሥራው ባሻገር በማኅበረሰብ ተኮር ሥራዎች የበለጠ መሥራት አለበት ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ፡፡

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸውም÷ ዩኒቨርሲቲው ከአካዳሚክ ሥራው ጎን ለጎን ግቢዎቹን በአትክልትና ፍራፍሬ ለማስዋብ ያደረገውን ጥረት ተመልክተዋል።

ዩኒቨርሲቲው የጀመረው ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸው÷ በሚያከናውነው የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ሥራ ከራሱ አልፎ የአካባቢውን ማኅበረሰብ ተጠቃሚ ማድረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው ባሻገር በማኅበረሰብ ተኮር ሥራዎች የበለጠ መሥራት እንዳለበት መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.