Fana: At a Speed of Life!

በለይቶ ማቆያ ማዕከላት ለሚቆዩና ወጪያቸውን መሸፈን ለማይችሉ ዜጎች መንግስት ሙሉ ወጪያቸውን ይሸፍናል – ኢንጂነር ታከለ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 14 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢንጂነር ታከለ ኡማ ከኢትዮጵያ ውጭ የነበሩ ወገኖች በሚመለሱበት ጊዜ ወደ ህብረተሰቡ ከመቀላቀላቸው በፊት በለይቶ ማቆያ ማዕከላት በሚቆዩባቸው ጊዜዎች ወጪያቸውን መሸፈን ለማይችሉ ዜጎች ሙሉ ወጪያቸውን መንግስት እንደሚሸፍን አስታወቁ።

ኢንጂነር ታከለ በፌስ ቡክ ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ መንግስት ከተለያዩ ሃገራት ወደ ኢትዮጵያ ለሚገቡ መንገደኞች እና ወገኖች የለይቶ ማቆያ ማዕከል ማዘጋጀቱን አስታውቀዋል።

በዚህ ወቅትም ለቆይታ ጊዜው ወጪያቸውን መሸፈን ለማይችሉ ዜጎች የከተማ አስተዳደሩ ሙሉ ወጪያቸውን እንደሚሸፍን ገልጸዋል።

ኢንጂነር ታከለ አያይዘውም በመተሳሰብ ራስን መጠበቅ እንደሚገባ ጠቅሰዋል።

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.