Fana: At a Speed of Life!

ትኩረቱን በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ያደረገ ስብሰባ በጂቡቲ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ የምትሳተፍበት ትኩረቱን በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ያደረገ ስብሰባ በጂቡቲ እየተካሄደ ነው፡፡

ስብሰባው የጅቡቲው ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ በይፋ አስጀምረዋል፡፡

በሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዷለም የተመራ ልዑክ በስብሰባው እየተሳተፈ ነው፡፡

ስብሰባው “የአየር ንብረት ለውጥ እና ምርምር እንዲሁም ለዘላቂ መላመድ እና የመቋቋም መንገድ” በሚል ርዕስ እየተካሄደ መሆኑን በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.